የአሊባባ የግብይት ማዕከል ምን ጥቅሞች ይዞ ይመጣል?
Listen now
Description
የቻይናው አሊባባ ግሩፕ የዓለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክስ የግብይት ማዕከልን በኢትዮጵያ ለመመስረት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር ህዳር 15 ተፈራርሟል። “ንግድና ዲጂታል ኢኮኖሚን የሚያበረታታ ነው” የተባለለት ማዕከሉ የላቀ ቴክኖሎጂ፣ መሰረተልማት፣ አገልግሎት አሰጣጥና የቁጥጥር ማዕቀፍ እንደሚኖረው ተገልጿል።
More Episodes
በኢትዮጵያ የኤሌክትሮኒክ ግብይት የተሰማሩ ጀማሪ ኩባንያዎች ብቅ ብቅ እያሉ ነው። ከእነዚህ አንዱ የሆነው አስቤዛ መተግበሪያውን ወይም ድረ-ገጹን በመጠቀም ከመደብሮች እንጀራና የባልትና ውጤቶችን ጨምሮ የተለያዩ ነገሮች ለሚገዙ ደንበኞች ካሉበት ያደርሳል። የኩባንያው መሥራች በረከት ታደሰ አስቤዛ እንደ አማዞን የራሱ መደብር እንዲኖረው ይመኛል
Published 05/05/21